Login
Main menu

ትምህርቶች በጽሁፍ

ገብር ሔር

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! ገብር ሔር፡- ይህች ዕለት ከልዑል እግዚአብሔር የተለያያ ጸጋን(ሥጦታን) የተቀበልን ሁሉ አንደየሥራችን ምንሞገስባት አልያም የምንወቀስባት ዕለት ናት፡፡ ሁለቱም ለጥቅማችን እንጂ ለጥፋታችን አይደለም፡፡ ምስባክ፡- ከመ እንግር ፈቃደከ መከርኩ አምላኪየ ወሕግከኒ በማዕከለ ከርሥየ ዜኖኩ ጻድቀከ በማኅበር ዐቢይ፤ መዝ ፴፱፡፰ ትርጉም፡- አምላኬ ሆይ ፈቃድህን እገልጥ(አደርግ) ዘንድ ወደድሁ ሕግህም በልቤ ውስጥ ነው፤ በታላቅ ጉባኤ ጽድቅህን አወራሁ፡፡ - አምላኬ ሆይ ፈቃድህን ቃል ከግብር አስማምቼ እገልጣት ዘንድ ወደድሁ፡፡ እንዲህ የተዋቡ ቃላትና ሀሳቦች ሊፈልቁ የሚችሉት ከእግዚአብሔር ፈቃድ ጋር ህብረት ካደረጉ ልቦች(አልባብ)ብቻ ነው፡፡ከሁሉ አስቀድሞ የጌታ እግዚአብሔር ፍቃዱ ምን እንደሆነ አውቃ ትገዛለት ዘንድ ነፍስ በትህትና ወደ ቃሉ ማዕድ መቅረብ ያስፈልጋታል፡፡ ጌታም በመጽሐፍ…
Read more...

ደብረዘይት

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! የቀጠለ... ፭.ደብረዘይት፡- በዚህ ዕለት በቤተክርስቲያን ነገረ ምፅዓቱ ይታሰባል፡፡ ደብረዘይት ይህንኑ እውነታ ጌታ ለሐዋርያት ያስታወቀበት ተራራ ነው፡፡ ዳግመኛም መምጣቱ በዚሁ ተራራ እንደሆነ ይታመናል፡፡ ምስባክ፡- እግዚአብሔርሰ ገሃደ ይመፅዕ ወአምላክነሂ አያረምም እሳት ይነድድ ቅድሜሁ ትርጉም፡- እግዚአብሔር ግልጥ ሆኖ ይመጣል አምላካችን ይመጣል ዝምም አይልም እሳት በፊቱ ይቃጠላል መዝ ፵፱፥፪ - ይህ ሀይለ ቃል ለቀዳማዊውም ለዳግም ምፅዓቱም ይነገራል፡፡ - በቀዳማዊ ምፅዓቱ ግልጥ ሆኖ ይመጣል ሲል፤ በባህርዩ የማይታይ የማይዳሰስ ሲሆን ከእመቤታችን በነሣው ሥጋ የሚታይ የሚዳሰስ ሆኖ ምጣቱን ሲያጠይቅ ነው፡፡ እሳት ይነዳል ማለቱ አልመለስ ካሉ ፈርዶ የሚያጠፋበት ሥልጣኑ የባህርዩ መሆኑን ያሳያል፡፡ ማቴ 23 - ለደዳግም ምፅዓቱ ግልጥ ሆኖ ይመጣል…
Read more...

የተሻለ ምርጫ

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! በተለያየ አህጉር አንድ ጊዜ ስለተሠጠች የቅዱሳን ሃይማኖት እየተጋደላችሁ፤ ዲያብሎስንና ሥራውን ሁሉ በእምነት ኃይል እየተቃወማችሁ የጌታችንን የአምላካችንንና የመድኃኒታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን ዳግም መምጣት በተስፋ ለምትጠባበቁ የመንፈስ ልጆቼ የተላከ አእምሮን ሁሉ የሚያልፍ የእግዚአብሔር ሰላም ከሁላችሁ ጋር ይሁን! ባለፉት ጊዜያቶች በላክሁላችሁ ጦማሮች ቅዱስ እግዚአብሔርን በመከተልና፤በቅድስና ስፍራው በቤቱ በመገኘት የምናገኘውን መልካም ነገርና፤ ምርጫችንም ምን መሆን እንዳለበት ተነጋግረናል፡፡ ለዛሬ እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ በገለጠልን መጠን ሌላ ሦስተኛ ጠቃሚ ነጥብ አናያለን፡፡ ከብዙ ወርቅና ብር ይልቅ የአፍህ ሕግ(ቃል) ይሻለኛል መዝ118፥70 ነብዩ ዳዊት በዚህ የመዝሙር ቃሉ ሁለት በሰው ዘንድ ከፍተኛ ትኩረት የሚስቡ (የሚወደዱ) እንዲሁም አስፈላጊ የሆኑ ነገሮችን አነፃጽሯል፡፡ አንዱ ጊዜያዊ ሌላው ዘላለማዊ፣…
Read more...

...በዋዘኞችም ወንበር ያልተቀመጠ ብፁዕ ነው፡፡ መዝ ፩፡፩

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን፡፡ በክፉዎች ምክር ያልሄደ በኃጢአተኞችም መንገድ ያልቆመ በዋዘኞችም ወንበር ያልተቀመጠ ብፁዕ ነው፡፡ መዝ ፩፡፩ በመዝሙረ ዳዊት የተመሰገኑ ጠባይዓትንና አካሄዶችን አመለካከቶችንና ተግባራትን “ብፁዕ” በሚል የውዳሴ ቃል እያጀበ ተቀኝቶ እናገኛለን፡፡ ብፁዕ የሚለው ቃል “በፅዐ” ከሚለው የግዕዝ ግሥ የሚወጣ ሲሆን የተደነቀ የተመሰገነ ንዑድ ክቡር የሚለውን ትርጉም ይይዛል፡፡ ከላይ በተቀመጠው ጥቅስ ክቡር ዳዊት ሦስት አንድን ሰው ወደ ጥፋት የሚወስዱ ጉዳዩችን አንስቶ ከእነርሱ በተቃራኒ የሚገኝ ቢኖር ንዑድ ክቡር ነው ይለናል፡፡ ቀዳሚው በክፉዎች ምክር ያልሄደ ብፁዕ(ምስጉን) ነው ይላል፡፡ ምክር አንድን ሰው ክፉውን ጠባይዕ እንዲተው መልካሙን ደግሞ እንዲያፀና አስነዋሪ ተግባር የበጀ መስሎት የሚኖር ካለ እንዲመለስ፤ የተወደደ ሥራ ለመሥራት መንገድ የጠፋውንም…
Read more...

ስለጌታችን አምላካችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ: ክፍል ስምንት

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን በተለያዩ አህጉር ተበትናችሁ በቃሉ ለመኖር ለምትጋደሉ የመንፈስ ልጆቼ የተላከ ህሊናን ሁሉ የሚያልፍ የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ሰላም ከሁላችሁ ጋር ይሁን! ክርስቶስ ተንሥአ እሙታን በሚል ቃለ ብሥራት ሰላምታችንን እያስቀደምንና በትንሣኤው ትንሣኤያችንን እያወጅን ሰነበትን፡፡ “በማለዳ ምሕረትህን እንጠግባለን በዘመናችን ሁሉ ደስ ይለናል ሐሤትም እናደርጋለን መከራ ባሳየኸን ዘመን ፈንታ ክፉም ባየንባቸው ዘመኖች ፈንታ ደስ ይለናል፡፡” እንዳለ ነቢዩ ዳዊት ፍርድህን ከሰማንበት ቃልህ፤ ምህረትህን ፣ ይቅርታህን ፤በሞት አዋጆች ፈንታ ትንሣኤና ሕይወትን፤ከባርነት ተላቀን ነፃነትን በመቀዳጀታችን የመከራውን ዘመን አስረስተህ ደስታን ሞላኸን፡፡ ከዛሬ ፪ሺ ዓመት ገደማ የበዛልን ሥጦታህ ከአበው ወደ ውሉድ እየተላለፈ ደስታው ሳይፈዝ ስሜቱ ሳይደበዝዝ “ግበሩ በዓለ በትፍስህት” እንዲል ዛሬም እንደያኔው…
Read more...

ስለጌታችን አምላካችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ: ክፍል ሰባት

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! መግቢያ፡ በተለያዩ አህጉር ተበትናችሁ በቃሉ ለመኖር ለምትጋደሉ የመንፈስ ልጆቼ የተላከ ህሊናን ሁሉ የሚያልፍ የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ሰላም ከሁላችሁ ጋር ይሁን! ሌላው ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ የባህርይ አምላክነቱን ከገለፀባቸው ባህርያት አንዱ ኃጢአትን የማስተሰረይ(ይቅር የማለት) ሥልጣኑ ነው፡፡ በመጽሐፍ እንደተፃፈ ኃጢአትን ማስተሰረይ ብቸኛ የቅዱስ እግዚአብሔር ሥልጣን ነው፡፡ በማር.ወን 2፥ 5፡- ላይ ሽባውን ሰው እንዲፈውስላቸው በአልጋ አድርገውና የቤቱን ክዳን ነቅለው በጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ፊት ሲያቀርቡት አንተ ሰው ኃጢአትህ ተሰረየችልህ ነበር ያለው፡፡ በዚያ የነበሩ አይሁድም "ይህ ሰው በርግጥ ይሳደባል ከአንዱ ከእግዚአብሔር በቀር ኃጢአትን ያስተሰርይ ዘንድ ማን ይችላል?" በማለት ሲያጉረመርሙ ጌታችን ግን "የሰው ልጅ ኃጢአትን ያስተሰርይ ዘንድ ሥልጣን እንዳለው…
Read more...
Subscribe to this RSS feed

ጠቃሚ አድራሻዎች

መጻሕፍት ቢያነቧቸው

  • * ​ፍቅር 
  • ፍና ቅዱሳን
  • * የቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ሕይወቱ እና ትምህርቱ 
  • * ዝጎራ