በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! የቀጠለ... ፭.ደብረዘይት፡- በዚህ ዕለት በቤተክርስቲያን ነገረ ምፅዓቱ ይታሰባል፡፡ ደብረዘይት ይህንኑ እውነታ ጌታ ለሐዋርያት ያስታወቀበት ተራራ ነው፡፡ ዳግመኛም መምጣቱ በዚሁ ተራራ እንደሆነ ይታመናል፡፡ ምስባክ፡- እግዚአብሔርሰ ገሃደ ይመፅዕ ወአምላክነሂ አያረምም እሳት ይነድድ ቅድሜሁ ትርጉም፡- እግዚአብሔር ግልጥ ሆኖ ይመጣል አምላካችን ይመጣል ዝምም አይልም እሳት በፊቱ ይቃጠላል መዝ ፵፱፥፪ - ይህ ሀይለ ቃል ለቀዳማዊውም ለዳግም ምፅዓቱም ይነገራል፡፡ - በቀዳማዊ ምፅዓቱ ግልጥ ሆኖ ይመጣል ሲል፤ በባህርዩ የማይታይ የማይዳሰስ ሲሆን ከእመቤታችን በነሣው ሥጋ የሚታይ የሚዳሰስ ሆኖ ምጣቱን ሲያጠይቅ ነው፡፡ እሳት ይነዳል ማለቱ አልመለስ ካሉ ፈርዶ የሚያጠፋበት ሥልጣኑ የባህርዩ መሆኑን ያሳያል፡፡ ማቴ 23 - ለደዳግም ምፅዓቱ ግልጥ ሆኖ ይመጣል…
Read more...