Login
Main menu

የባሕርይ መጎስቆል( ሰሞነኛው ጉዳይ)

 

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!

“ንግር ወኢተአርምም!”

                                                  የሐዋ.ሥራ 18፡9

 

ሰሞኑን እመቤታችን ‘የአዳምን የጎሰቆለ ባሕርይ’ ነው የያዘችው ብሎ ከተናገረ አንድ ወንድማችን ጋር የተደረገ የቃላት ምልልስን አንዳንድ የቤተ ክርስቲያን ልጆች ጉዳዩ አሳስቧቸው አጋሩኝ። ከውይይቱ የተገነዘብሁት ነገር መልስ ይሰጥበት የነበረው የጥያቄውን ዐውድ በተረዳ መንገድ አለመሆኑን ነው። ውይይቱ በአብዛኛው ያተኮረው ስለ ጥንተ አብሶ፣ ስለ መርገም፣ ስለ ጎሰቆለ ባሕርይ እንጂ ይህ ባሕርይ እንዴት ታደሠ? እግዚአብሔር የአዳምን የጎሰቆለ ባሕርይ ለማደስ ወደ ቀደመ ክብሩም ለመመለስ ምን አደረገ? የሚለውን ከነገረ ድኅነት አንጻር አልነበረም።

ከቤተ ክርስቲያን ታሪክ እንደምንረዳው እንዲህ ዓይነት ጠንከር ያሉ ዶግማ ነክ ጉዳዮች ላይ መወያየት ለቤተ ክርስቲያን አዲስ አይደለም። የነበረ ያለና ወደ ፊትም የሚኖር ነው። አሁን ያሉ የቤተ ክርስቲያን ሊቃውንትም ጉዳዩ ላይ አጥጋቢ ምላሽ በማቅረብ ሁሉን ወደ ቦታው መመለስ ይጠበቅባቸዋል። እኔም እንደ ቤተ ክርስቲያን ልጅነቴ የራሴን ጥያቄና ሀሳብ ከዚህ እንደሚከተለው ለማሳየት እሞክራለሁ።

Read more: የባሕርይ መጎስቆል( ሰሞነኛው ጉዳይ)

ጠቃሚ አድራሻዎች

መጻሕፍት ቢያነቧቸው

  • * ​ፍቅር 
  • ፍና ቅዱሳን
  • * የቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ሕይወቱ እና ትምህርቱ 
  • * ዝጎራ